በአሏህ ስም እጅግ በጣም ርህሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
=<({አል-ኢኽላስ 112:1-4})>=
ﺑﺴﻢ ﺍﻟﻠﻪ ﺍﻟﺮﺣﻤﻦ ﺍﻟﺮﺣﻴﻢ
1. በል! እርሱ አላህ አንድ ነው።
2. አላህ (የሁሉ) መጠጊያ ነው።
3. አልወለደም፤ አልተወለደምም።
4. ለእርሱም አንድም ብጤ የለውም።

 =<({አል-ቁርአን 96:1-5})>=
ያ ሁሉን በፈጠረው ጌታህ ስም አንብብ!
በቡኻሪ በተዘገበው ሐዲስ መሰረት እውቀትን መሻት በእያንዳንዱ ሙስሊም ላይ ግዴታ ነው።  |
:☀:ከአንጀት ካለቀሱ እንባ አይገድም:☀:
መስተካከልን አስበን ወደ አሏህ ለመመለስ ከቆረጥን አሏህ በባሮቹ ላይ አይጨክንም። የውሸት ኑሮን አንኑር ወደ አሏህ(ሱ.ወ.ተ) ብንመለስ ነው የሚሻለው።
እንስተካከል ነገሮች ሁሉ ይስተካከሉልናል። ከህይወት ወከባ እናርፋለን፤ ወደ ማይቀረው አለም ስንሄድ አንፈራም እንደፍራለን። መስተካከል የአሏህ እዝነት ነው። ጥመት ደግሞ የእሱ ቁጣ ነው። ለዚህም ነው በግዴታ ሶላቶቻችን ብቻ በቀን 17 ጊዜ አሏህን ቀጥተኛውን ጎዳና ይመራን ዘንድ የምንለምነው።
አሏህ በቁርአኑ በሱረቱል ፋቲሃ ከአንቀፅ 6-7 ባለው እንዲህ ይላል:-
=<({አል-ቁርአን 1:6-7})>=
{6} ቀጥተኛውን መንገድ ምራን
{7} የእነዚያን በእነርሱ ላይ በጎ የዋልክላቸውን በእነሱ ላይ ያልተቆጣህባቸውንና ያልተሳሳቱትንም ሰዎች መንገድ ምራን።
ዱንያ አስቸጋሪ ድልድይ ናት። መሰናክሎች ፣ ጉቶዎችና መንጠቆዎች ይበዙባታል። ስሜት ፣ ስጋ ፣ ነፍስ ፣ ሸይጧን ፣ ሰዎችም ጭምር መልካሙን ሰው ከመልካም ጎዳና ለማውጣት ከዚህም ከዚያም ይመነታትፉታል። ታዲያ የነገን አስቸጋሪ የጀሃነም ድልድይ ልናልፍ የምንችለው የዱንያን ድልድይ በብቃት ስንሻገር ነው።
እናም ውድ ሙስሊም እህት ወንድሞቼ ወደ ቁርአን ወደ ሱና እንመለስ። እራስችንን እናስተካክል። መስለን ከመታየት ይልቅ ሆነን መገኘትን ምርጫችን እናድርግ። ምንግዜም ዱአ ባደረግን ቁጥር ያ-ረቢ ጌታየ ቀጥተኛውን መንገድ ከመራሃቸው ባሪያውችህ መካከል አድርገኝ ማለትን አንዘንጋ።
©የወጣቱ ተልእኮ
۩Youth-Mission
የወጣቱ ተልእኮ-> page۩
page:
http://facebook.com/youth.mission29
website:
http://youth-mission.mobie.in
'~'-.,__,.-'~'
_,.-'~''~'-.,_
482